This company has no active jobs
Company Information
- Total Jobs 0 Jobs
- Location Addis Ababa
About Us
በላይነህ ክንዴ (ቢኬ) ግሩፕ በሥሩ በማኑፋክቸሪንግ፣ኢምፖርት ኤክስፖርት፣እርሻ፣ሆቴል፣ ኮንስትራክሽን፣ ትራንስፖርትና ትራንዚት ዘርፎች የተሠማሩ ድርጅቶችን አቅፎ የያዘ ሲሆን በእነዚህም ዘርፎች ለበርካታ ዓመታት ተቀዳሚ አፈፃፀም በማስመዝገብ ለሀገር ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እድገት የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ይገኛል፡፡በማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ ላይ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ ፊቤላ ኢንዱስትሪያል ኃ/የተ/የግ/ማህበርን በማቋቋም በሚል ስም በአማራ ክልል በምዕራብ ጎጃም ዞን በቡሬ ከተማ ያቋቋማቸዉ የአግሮ ኢንዱስትሪ ስራ መስራት የሚያስችሉ ግንባታዎችን አጠናቆ ስራ እንደሚጀምር ስንገልጽ በታላቅ ደስታ ነዉ፡፡ ይህ በቡሬ የሚገኘዉ ግዙፉ የምግብ ዘይት ፋብሪካ በቀን እስከ 1400 ቶን (1.5 ሚሊዮን ሊትር) የምግብ ዘይት፣ የአትክልት ቅቤ፣ ማርጋሪንና የሳሙና ምርቶችን የሚያመርት ሲሆን በዚህም በከፍተኛ ደረጃ የአገሪቱን የምግብ ዘይት ፍላጎት እንደሚያሟላና የዉጭ ምንዛሪ እንደሚያድን ይጠበቃል፡፡ የሰሊጥ ማቀነባበሪያ ፋብሪካውም በቀን እስከ 480 ቶን ሰሊጥ እጅግ በጣም ከፍተኛ ጥራቱን የጠበቀ የተበጠረ፣ የተፈተገና የተቆላ የሰሊጥና ጣሂና ምርቶችን ለአለመቀፍ ገበያ ያቀርባል፡፡